Telegram Group & Telegram Channel
የድንግል መወለድ

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

ሃናና ኢያቄም ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ ! ልጅን ለቤት ሳይሆን ለዓለም ወለዳችሁ ። ቡሩክ ማኅፀን ያለሽ ሃና ሆይ ! ያለ ዘር ያለ ሩካቤ የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ። የልጅ ልጅ ለማየት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ችሎታ በቤተሰብሽ ለማየት ሃና ሆይ በስእለት ድንግልን ወለድሽ ! ከእግዚአብሔር የተገኘችውን ለእግዚአብሔር ሰጠሽ ። ከእግዚአብሔር ተገኝታ ፣ በእግዚአብሔር የኖረች ልጅ ወለድሽ ! ውስጣዊ ደም ግባት ያላትን ልጅ ወለድሽ ! እግዚአብሔር የሚያየውን ውበት የተጎናጸፈች ልጅ ወለድሽ ! አዳም በገነት በተስፋ ያያትን ፣ ያችን ሴት ያለ ወንድ ዘር የምትፀንሰውን ድንግል ወለድሽ ! የፀሐዩ የክርስቶስ እናት ምሥራቅ ማርያም ካንቺ ተወለደች ። እውነተኛው ኮከብ የተወለደባት ፣ ምድራዊ ክፋት ያልቀረባት ሰማይ ዛሬ ተወለደች ። ሃና ሆይ ኢሳይያስ የተናገረውን ትንቢት ሰምተሽ ነበር ። ያ ትንቢት በእኔ ይፈጸማል ብለሽ አልጠበቅሽም ። እግዚአብሔር ግን አሳቡን በጊዜው ይፈጽማልና ድብቅ በረከት ድንግልን ዛሬ ወለድሽ !

በስደት ዓለም ላይ ድርብ ስደት የገጠመሽ ፣ በሊባኖስ ተራሮች የአርዘ ሊባኖሱን የዘንካታውን የክርስቶስን እናት ወለድሽ ! ለአምላክ አያት እሆናለሁ ብለሽ አስበሽ አታውቂም ነበር ። ቡሩክ ልጅ ስትለምኚ አምላክን የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ! ሃና ሆይ በሕግ በሩካቤ ልጅን ወለድሽ ፣ ካንቺ የተወለደችው ድንግል ግን ከሕግ በላይ በሥልጣነ እግዚአብሔር በድንግልና ፀንሳ የምትወልድ ሆነች ። ላንቺ ጋብቻ ክብርሽ ነበር ፣ ለልጅሽ ድንግል መሆን ክብርዋና መጠሪያዋ ነው ። አንቺ እስከ ጊዜው ድንግል ነበርሽ ፣ ልጅሽ ግን ለዘላለም ድንግል ናት ። አንቺ ቤተሰቦችሽ ለወንድ አጩሽ ፣ ልጅስ ማርያም ግን አብ ለልጁ ማደሪያ እንድትሆን መረጣት ። አንቺ አምላክን በእምነት አየሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን በባሕርይ ልደት ወለደችው ። አንቺ ካንቺ በኋላ ያለች ልጅን ወለድሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን የሚቀድማትን ልጅ ወለደች ። ሃና ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! የወለደም ያልወለደም በሚያዝንበት በዚህ ጎዶሎ ዓለም ሙሉ ጨረቃ ማርያም ካንቺ ተወለደች ።

ኢያቄም ሆይ ደስ ይበልህ ! የአብራክህ ክፋይ ድንግል ማርያም የባሕርያችን መመኪያ ሆነች ። ሰውና እግዚአብሔር የ5500 ዘመን ቀጠሮአቸውን በድንግል ማርያም ማኅፀን ፈጸሙ ። ምሳሌው አማናዊ የሚሆንባት ፣ ትንቢት የሚያርፍባት ፣ ንግርት የሚጠናቀቅባት ፣ ሱባዔ የሚቋጭባት ድንግል ዛሬ ተወለደች ። ክብርህ ከታላላቅ አባቶች ነው ። የዳዊት ልጅ መሆን ካኮራህ ፣ የዳዊት አምላክ ካንተ በመወለዱ እንዴት አትኮራም !! ለአምላክ አያት ለመሆን የበቃህ ኢያቄም በእውነት የተባረክህ ነህ ። እናንተ ዘረ ቅዱሳን ከአብርሃም እስከ ዳዊት ፣ ከዳዊት እስከ ኤልሳቤጥ ፣ ከሃና እስከ ድንግል ቅድስና አልነጠፈባችሁም የታደላችሁ ናችሁ ። ምነው የእናንተ ዘመድ ባደረገኝ !

የሰጪው እናት ከሁሉ ይልቅ ድሀ ነሽ ፣ ነገር ግን እንዳንቺ የበለጸገ ማንም የለም ። የቸሩ እናት አዛኝ ነሽ ፣ እንዳንቺ የሆነለት ማንም የለም ፣ ነገር ግን በበረት የወለድሽ ፣ በግብጽ የተሰደድሽ ነሽ ። ሕይወትሽ ቅኔ የሆነው ፣ ባንቺ ላይ ያለው ምሥጢር የማይፈታው የኢየሱስ እናት ማርያም እንኳን ተወለድሽ ! በመወለድሽ ብዙ ነገር እንማራለን ። እግዚአብሔር ጋብቻን እንደሚያከብር ከወላጆችሽ ተማርን ። ድንግልናን እንዳከበረ ካንቺ ተማርን ። እግዚአብሔር ለሚጠብቁት ቸር መሆኑን በስእለት በመወለድሽ አወቅን ። አንቺ ልጅሽን በበረት ብትወልጅ ፣ ያንቺ ልደትም በስደት በሊባኖስ ተራራ ላይ ሆነ ። ዓለም ለደግና ለደጎች ደግ ለክርስቶስ እንደማትሆን ተማርን ። አንቺን የመሰለች ልጅ ቢያገኙም ለእግዚአብሔር ሰጡ እንጂ የራሳቸው አላደረጉሽም ። እግዚአብሔር ጋ የተቀመጠ የት ይሄዳል ? ብለው ሰጡሽ ። መቅደስ ሆይ በመቅደስ አደግሽ ። አሮን ከገባባት ከቅድስተ ቅዱሳን የምትበልጪ የታላቁ ሊቀ ካህን የክርስቶስ መቅደስ ሆይ እሰይ ተወለድሽልን ። ድንግል ሆይ የልደትሽ በረከት ይድረሰን ። ኃጢአት ላደከመን ልጆችሽ ምልጃሽ አይለየን !

ሁሉን አዋቂ ወልድ ሆይ! ስለ ወዳጅህ ስለ አብርሃም ከማለት ስለ እናት ስለ ድንግል ማለት ይበልጣልና ። ከወዳጅ እናት ትልቃለችና ። ስለ አማኑኤል ስምህ ስለ ማርያም እናትህ ብለህ በዓይነ ምሕረት ተመልከተን ! ማዕበሉን ቀዝፈህ አሻግረን !

እንኳን ለድንግል ማርያም ልደት አደረሳችሁ!

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3940
Create:
Last Update:

የድንግል መወለድ

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

ሃናና ኢያቄም ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ ! ልጅን ለቤት ሳይሆን ለዓለም ወለዳችሁ ። ቡሩክ ማኅፀን ያለሽ ሃና ሆይ ! ያለ ዘር ያለ ሩካቤ የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ። የልጅ ልጅ ለማየት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ችሎታ በቤተሰብሽ ለማየት ሃና ሆይ በስእለት ድንግልን ወለድሽ ! ከእግዚአብሔር የተገኘችውን ለእግዚአብሔር ሰጠሽ ። ከእግዚአብሔር ተገኝታ ፣ በእግዚአብሔር የኖረች ልጅ ወለድሽ ! ውስጣዊ ደም ግባት ያላትን ልጅ ወለድሽ ! እግዚአብሔር የሚያየውን ውበት የተጎናጸፈች ልጅ ወለድሽ ! አዳም በገነት በተስፋ ያያትን ፣ ያችን ሴት ያለ ወንድ ዘር የምትፀንሰውን ድንግል ወለድሽ ! የፀሐዩ የክርስቶስ እናት ምሥራቅ ማርያም ካንቺ ተወለደች ። እውነተኛው ኮከብ የተወለደባት ፣ ምድራዊ ክፋት ያልቀረባት ሰማይ ዛሬ ተወለደች ። ሃና ሆይ ኢሳይያስ የተናገረውን ትንቢት ሰምተሽ ነበር ። ያ ትንቢት በእኔ ይፈጸማል ብለሽ አልጠበቅሽም ። እግዚአብሔር ግን አሳቡን በጊዜው ይፈጽማልና ድብቅ በረከት ድንግልን ዛሬ ወለድሽ !

በስደት ዓለም ላይ ድርብ ስደት የገጠመሽ ፣ በሊባኖስ ተራሮች የአርዘ ሊባኖሱን የዘንካታውን የክርስቶስን እናት ወለድሽ ! ለአምላክ አያት እሆናለሁ ብለሽ አስበሽ አታውቂም ነበር ። ቡሩክ ልጅ ስትለምኚ አምላክን የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ! ሃና ሆይ በሕግ በሩካቤ ልጅን ወለድሽ ፣ ካንቺ የተወለደችው ድንግል ግን ከሕግ በላይ በሥልጣነ እግዚአብሔር በድንግልና ፀንሳ የምትወልድ ሆነች ። ላንቺ ጋብቻ ክብርሽ ነበር ፣ ለልጅሽ ድንግል መሆን ክብርዋና መጠሪያዋ ነው ። አንቺ እስከ ጊዜው ድንግል ነበርሽ ፣ ልጅሽ ግን ለዘላለም ድንግል ናት ። አንቺ ቤተሰቦችሽ ለወንድ አጩሽ ፣ ልጅስ ማርያም ግን አብ ለልጁ ማደሪያ እንድትሆን መረጣት ። አንቺ አምላክን በእምነት አየሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን በባሕርይ ልደት ወለደችው ። አንቺ ካንቺ በኋላ ያለች ልጅን ወለድሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን የሚቀድማትን ልጅ ወለደች ። ሃና ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! የወለደም ያልወለደም በሚያዝንበት በዚህ ጎዶሎ ዓለም ሙሉ ጨረቃ ማርያም ካንቺ ተወለደች ።

ኢያቄም ሆይ ደስ ይበልህ ! የአብራክህ ክፋይ ድንግል ማርያም የባሕርያችን መመኪያ ሆነች ። ሰውና እግዚአብሔር የ5500 ዘመን ቀጠሮአቸውን በድንግል ማርያም ማኅፀን ፈጸሙ ። ምሳሌው አማናዊ የሚሆንባት ፣ ትንቢት የሚያርፍባት ፣ ንግርት የሚጠናቀቅባት ፣ ሱባዔ የሚቋጭባት ድንግል ዛሬ ተወለደች ። ክብርህ ከታላላቅ አባቶች ነው ። የዳዊት ልጅ መሆን ካኮራህ ፣ የዳዊት አምላክ ካንተ በመወለዱ እንዴት አትኮራም !! ለአምላክ አያት ለመሆን የበቃህ ኢያቄም በእውነት የተባረክህ ነህ ። እናንተ ዘረ ቅዱሳን ከአብርሃም እስከ ዳዊት ፣ ከዳዊት እስከ ኤልሳቤጥ ፣ ከሃና እስከ ድንግል ቅድስና አልነጠፈባችሁም የታደላችሁ ናችሁ ። ምነው የእናንተ ዘመድ ባደረገኝ !

የሰጪው እናት ከሁሉ ይልቅ ድሀ ነሽ ፣ ነገር ግን እንዳንቺ የበለጸገ ማንም የለም ። የቸሩ እናት አዛኝ ነሽ ፣ እንዳንቺ የሆነለት ማንም የለም ፣ ነገር ግን በበረት የወለድሽ ፣ በግብጽ የተሰደድሽ ነሽ ። ሕይወትሽ ቅኔ የሆነው ፣ ባንቺ ላይ ያለው ምሥጢር የማይፈታው የኢየሱስ እናት ማርያም እንኳን ተወለድሽ ! በመወለድሽ ብዙ ነገር እንማራለን ። እግዚአብሔር ጋብቻን እንደሚያከብር ከወላጆችሽ ተማርን ። ድንግልናን እንዳከበረ ካንቺ ተማርን ። እግዚአብሔር ለሚጠብቁት ቸር መሆኑን በስእለት በመወለድሽ አወቅን ። አንቺ ልጅሽን በበረት ብትወልጅ ፣ ያንቺ ልደትም በስደት በሊባኖስ ተራራ ላይ ሆነ ። ዓለም ለደግና ለደጎች ደግ ለክርስቶስ እንደማትሆን ተማርን ። አንቺን የመሰለች ልጅ ቢያገኙም ለእግዚአብሔር ሰጡ እንጂ የራሳቸው አላደረጉሽም ። እግዚአብሔር ጋ የተቀመጠ የት ይሄዳል ? ብለው ሰጡሽ ። መቅደስ ሆይ በመቅደስ አደግሽ ። አሮን ከገባባት ከቅድስተ ቅዱሳን የምትበልጪ የታላቁ ሊቀ ካህን የክርስቶስ መቅደስ ሆይ እሰይ ተወለድሽልን ። ድንግል ሆይ የልደትሽ በረከት ይድረሰን ። ኃጢአት ላደከመን ልጆችሽ ምልጃሽ አይለየን !

ሁሉን አዋቂ ወልድ ሆይ! ስለ ወዳጅህ ስለ አብርሃም ከማለት ስለ እናት ስለ ድንግል ማለት ይበልጣልና ። ከወዳጅ እናት ትልቃለችና ። ስለ አማኑኤል ስምህ ስለ ማርያም እናትህ ብለህ በዓይነ ምሕረት ተመልከተን ! ማዕበሉን ቀዝፈህ አሻግረን !

እንኳን ለድንግል ማርያም ልደት አደረሳችሁ!

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3940

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Export WhatsApp stickers to Telegram on Android

From the Files app, scroll down to Internal storage, and tap on WhatsApp. Once you’re there, go to Media and then WhatsApp Stickers. Don’t be surprised if you find a large number of files in that folder—it holds your personal collection of stickers and every one you’ve ever received. Even the bad ones.Tap the three dots in the top right corner of your screen to Select all. If you want to trim the fat and grab only the best of the best, this is the perfect time to do so: choose the ones you want to export by long-pressing one file to activate selection mode, and then tapping on the rest. Once you’re done, hit the Share button (that “less than”-like symbol at the top of your screen). If you have a big collection—more than 500 stickers, for example—it’s possible that nothing will happen when you tap the Share button. Be patient—your phone’s just struggling with a heavy load.On the menu that pops from the bottom of the screen, choose Telegram, and then select the chat named Saved messages. This is a chat only you can see, and it will serve as your sticker bank. Unlike WhatsApp, Telegram doesn’t store your favorite stickers in a quick-access reservoir right beside the typing field, but you’ll be able to snatch them out of your Saved messages chat and forward them to any of your Telegram contacts. This also means you won’t have a quick way to save incoming stickers like you did on WhatsApp, so you’ll have to forward them from one chat to the other.

Nolawi ኖላዊ from in


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA